ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ የሚገኙ አርሶ አደሮችን ማሳ እየጎበኙ ነው

 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ የሚገኙ አርሶ አደሮችን ማሳ በመጎብኘት ላይ ናቸው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በበጋ መስኖ የለሙ የስንዴ ማሳዎችን እንደዚሁም የቡና ልማትን ነው በመጎብኘት ላይ የሚገኙት።

ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋርም በቀጠናው የዓለም ባንክ ዳይሬክተርና በተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና ሌሎች የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በመስክ ጉብኝቱ ላይ ተገኝተዋል።

በቴሌግራም ገጻችን ይቀላቀሉን


Post a Comment

አዲስ የድሮ